ለግብርና ኮሌጅ መካከከለኛ አመራሮችና መምህራን በመሪነት ክህሎት ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ።

ወሎ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ከግብርና ኮሌጅ ጋር በመተባበር በኮሌጁ በተለያዩ የስራ ክፍሎች በተለያዩ ሃላፊነት ቦታ ላይ ለሚገኙ አካላት በመሪነት ክህሎት ዙሪያ ለሶስት ቀናት ስልጠና ሰጥቷል።

በቢዝነስ እና ማኔጅመንት ኮሌጅ የማኔጅመንት ት/ክፍል ሃላፊ እና አሰልጣኝ ዶ/ር መንግስቱ ጉልቲ ስልጠናው ተግባቦት፣ ውሳኔ አሰጣጥ፣ ችግር አፈታት፣ ዘመኑን የዋጁ የመሪነት ጥበብ እና ክህሎት የሚሉ አንኳር ጉዳዮችን ያካተተ መሆኑን ገልጸው ስልጠናው የአመራርነትን አቅም ለማጎልበት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል።

ስልጠናው ዶ/ር መንግስቱን ጨምሮ የቢዝነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ዲን በሆኑት ዶ/ር ይመር አያሌው እና ከማኔጅመንት ት/ ክፍል መምህርት ዘሙ መሀመድ የተሰጠ ሲሆን በስልጠናው ማጠቃለያ ከተሳታፊዎች ለተሰነዘሩ አስተያየቶች መልስ የሰጡት ዶ/ር ይመር ስልጠናው በቀጣይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳውቀዋል።

Scroll to Top