Announcements
የወሎ ዩኒቨርሲቲ ነባሩና አዲሱ የስራ አመራር ቦርድ አባላት የመስክ ጉብኝትና የስራ ርክክብ አደረጉ።
June 09, 2022 News

የወሎ ዩኒቨርሲቲ ነባሩና አዲሱ የስራ አመራር ቦርድ አባላት የመስክ ጉብኝትና የስራ ርክክብ አደረጉ። ========+++++++++=========== ረቡዕ ሰኔ 1 ቀን 2014 ዓ.ም (ወዩ ህ/ግ) የወሎ ዩኒቨርሲቲ አዲሱ የስራ አመራር ቦርድ በትምህርት ሚኒስቴር በተደረገ አዲስ ምደባ ከሚያዚያ 1 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ሃላፊነቱ መሰጠቱ ይታወቃል። በመሆኑም ነባሩ የስራ አመራር ቦርድ አባላት የተሰጣቸውን ኃላነቶችንና ስራዎችን ለአዲሱ የስራ አመራር ቦርድ አባላት በይፋ በዛሬው እለት ሰኔ 1 ቀን 2014 ዓ.ም አስረክበዋል። ኃላፊነታቸውን ላስረከቡ የአመራር ቦርድ አባላት እውቅና እና ስንብት የተደረገ ሲሆን ለአዳዲስ የቦርድ አባላት የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። በርክክቡ ወቅት የቦርድ ሰብሳቢው ክቡር ዶ/ር አለሙ ስሜ እና የወሎ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር መንገሻ አየነ ተገኝተዋል። ነባሩ እና አዲሱ የስራ አመራር ቦርድ አባላት እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንትና ም/ፕሬዝዳንቶች በተገኙበት በ2015 ዓ. ም ስራ የሚጀምረውን የጢጣ ግቢ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ከጉብኝቱ በኋላ በተደረገ የጋራ ውይይት ዩኒቨርሲቲውን ለማሳደግ ከመቸውም ጊዜ በተሻለ በትብብርና በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ ታመኗል።