በወሎ ዩኒቨርሲቲ የኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ተማሪዎችን እያስመረቀ ነው።

Wollo University Graduation KIoT

ህዳር 3 ቀን 2015 ዓ.ም (ወዩ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ጽ/ቤት)

ዛሬ ህዳር 3 ቀን 2015 ዓ.ም በኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት በምህንድስና የትምህርት ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 1062 ወንዶች እና 332 ሴቶች በድምሩ 1394 ተማሪዎችን በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግር በማስመረቅ ላይ ይገኛል።

በእለቱ የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ የተከበሩ ዶ/ር አህመዲን መሃመድ፣ የዩኒቨርሲቲያችን የቦርድ አባላት፣ የዩኒቨርሲቲያችን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ የሴኔት አባላትና መምህራን ተገኝተዋል።

በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ የኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ዶ/ር መላኩ ታመነ የስራ ሪፖርት አቅርበዋል። የወሎ ዩኑቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር መንገሻ አየነም የእኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የዕለተ የክብር እንግዳ የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ የተከበሩ ዶ/ር አህመዲን መሃመድ ለተመራቂ ተማሪዎች የስራ መመሪያ አስተላልፈዋል። በንግግራቸውም “ይቺን በደምና በአጥንት የተከበረች ሃገር በላብና በድካም ጠብቃችሁ እንዲታቆዩዋት” ብለዋል።

ተመራቂ ተማሪዎች እንኳን ደስ ያላችሁ እንላለን። መልካም የስራ ዘመን እንድገጥማችሁም እንመኛለን።

Scroll to Top