ኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በኢንዱስትሪ ሙያተኞች የኢንተርንሺፕ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ኢንተርንሺፕ ለሚወጡ ተማሪዎች እንዲሰጥ አደረገ።

ኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በኢንዱስትሪ ሙያተኞች የኢንተርንሺፕ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ኢንተርንሺፕ ለሚወጡ ተማሪዎች እንዲሰጥ አደረገ።

ኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት 08/03/2015ዓ.ም

የኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በ2015 ዓ.ም 1ኛ ሴሚስተር ኢንተርንሺፕ ለሚወጡ ተማሪዎች የኢንተርንሺፕ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በኢንዱስትሪ ሙያተኞች እንዲሰጥ አድርጓል::

በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠ ላይ በአከባቢው ከሚገኙ አምስት ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች የመጡ ሙያተኞች በአሰልጣኝነት ተሳትፈዋል። ስልጠናውን የሰጡት የኢንዱስትሪ ሙያተኞች ተማሪዎች በኢንተርንሺፕ ቆይታቸው የሚተገብሩ ተግባራት እና ምን ላይ ማተኮር እንዳለባቸው አስገንዝበዋል::

በተጨማሪም ተማሪዎች በኢንተርንሺፕ ውጤታማ እንዲሆኑና ክህሎት ይዘው እንዲወጡ በኢንዱስትሪው ውስጥ አከባቢያቸውን በንቃት እንዲመለከቱና የሚሰሩትን ስራዎችን በእለት ፣ በሳምንት እና በወር መዝግቦ በመያዝ የኢንዱስትሪውን ምርት አመራረት፣ ጥራት እና አሰራር እንዲመረምሩ ተነግሯል።

Leave a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Scroll to Top