በወሎ ዩኒቨርሲቲ የተንታ አትሌቲክስ ማዕከል 3ኛውን የኢትዩጲያ የማሰልጠኛ ማዕከላት የአትሌቲክስ ሻምፒዮና የዋንጫ ባለቤት በመሆን አጠናቀቀ።

ሰኔ 17 ቀን 2015 ዓ.ም (ወሎ ዩኒቨርሲቲ ህዝብ ህንኙነት ዳይሬክተር ጽ/ቤት)

3ኛው የኢትዮጵያ ማሰልጠኛ ማዕከላት የአትሌቲክስ ሻምፒዮኛ ከሰኔ14-17/2015 ዓ.ም በአዲስ አበባ በወሎ ዩኒቨርሲቲ የተንታ አትሌቲክስ የበላይነት ተጠናቀቀ ።በስድስት የማሰልጠኛ ማዕከላት በተካሄደው ውድድር በወሎ ይንቨርሲቲ በወንድም በሴትም በአጠቃላይ ውጤት የሶስት ዋንጫ ባለቤት ሁኗል።
በዚህም መሰረት
በሴቶች

  1. 183 ነጥብ በማምጣት 1ኛ በወሎ ዩኒቨርሲቲ የተንታ አትሌቲክስ ማዕከል
  2. 163 ነጥብ በማምጣት 2ኛ የደብረ ብርሃን ማሰልጠኛ ማዕከል
  3. 135 ነጥብ በማምጣት የባሬ ማሰልጠኛ ማዕከል
    በወንዶች
  4. 193 ነጥብ በማምጣት በወሎ ዩኒቨርሲቲ ማሰልጠኛ ማዕከል
  5. 173 ነጥብ በማምጣት የሀገረሰላም ማሰልጠኛ ማዕከል
  6. 112 ነጥብ በማምጣት የደብረብረሃን ማሰልጠኛ ማዕከል
    በአጠቃላይ ውጤት በሴትም በወንድም
  7. 376 ነጥብ በማምጣት በወሎ ዩኒቨርሲቲ ማሰልጠኛ ማዕከል
  8. 275 ነጥብ በማምጣት የደብረብረሃን ማሰልጠኛ ማዕከል
  9. 255 ነጥብ በማምጣት ሀገረሰላም ማሰልጠኛ ማዕከል
    ውጤት አምጥተዋል።
    “እንኳን ደስ ያላችሁ”
Scroll to Top