በወሎ ዩኒቨርሲቲ ለከፍተኛ ትምህርት ተመራቂ ተማሪዎች ሲስጥ የነበረው አገር አቀፍ የመውጫ ፈተና (Exit examination) በሠላም ተጠናቋል

ሐምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም (ወሎ ዩኒቨርሲቲ ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ጽ/ቤት)

ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው የፈተና መርሃግብር መሰረት ከሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 7 ቀን 2015 ዓ.ም በወሎ ዩኒቨርሲቲ በደሴና በኮምቦልቻ ግቢ ሲሰጥ የነበረው የዩኒቨርሲቲ ማጠናቀቂያ የመውጫ ፈተና (Exit examination) ዛሬ ተጠናቋል።

የዩኒቨርሲቲያችን የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር አወል ሰይድ የፈተናውን መጠናቀቅ አስመልክክተው እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው የመውጫ ፈተናውን ለመስጠት በአደረገው ቅድመ ጥንቃቄና ዝግጅት መሰረት ያለምንም ችግር ተሰጥቶ ተጠናቋል ብለዋል።

ም/ፕሬዚዳንቱ አያይዘውም የዘንድሮ የመውጫ ፈተና የወሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው በሁለቱም ግቢዎች (ደሴና ኮምቦልቻ) ፈተናቸውን መውሰዳቸውን ገልጸው ለተፈታኝ ተማሪዎች መልካም ዕድል እንዲገጥማቸው ምኞታቸውን ገልጸዋል።

Scroll to Top